ኮንጎ - የጉዞ ማስታወሻ ፪
ከሰሞኑ አንድ ምሽት ላይ ከኪንሻሳ ወጣቶች ጋር የባጥ የቆጡን ሳወጋ ነበር፡፡ እንደአብዛኛው የሀገሪቱ ወጣቶች ሁሉ የአለም መጨረሻው ፈረንሳይ ድምበር ከሚመስላቸው ከእነዚህ ጓደኞቼ አንዱ ታድያ ድንገት በጨዋታው መሃል ስለ ኢትዮጵያ ሲያነሳ ቀልቤን ሰበስቤ ማዳመጥ ጀመርኩ፡፡ ከዚህ ቀደም በኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ቻይና ሲጓዝ በአዲስ አበባ በኩል ትራንዚት አድርጎ እንደነበር እና የአዲስ አበባ ቦሌ አየር ማረፊያ እጅግ ዘመናዊ እንደሆነ በአግራሞት ተናገረ፡፡ እኔም አጋጣሚውን በመጠቀም ኢትዮጵያ እንዴት እያደገች እንዳለች ለተቀሩት ማስረዳት ቀጠልኩ፡፡