Thursday, August 23, 2012

ሶስት ቀናት ሶስት ነገሮች (Aug 23, 2012)

(ባለፉት ሶስት ቀናት እየሁ ሰማሁ ታዘብኩ)

1.      ክፉም ሆነ ደግ፣ ደሃም ሆነ ሃብታም፣ ታሪክ ሰራም አልሰራም፣ ማንም ከሞት አያመልጥም፡፡ በአቡነ ጳውሎስ ህልፈት አይኑ ያልደረቀው የኢትዮጵያ ህዝብ ይኸው ጠቅላይ ሚኒስትሩንም አጣ፡፡ ባዶ ቤት ባዶ ቤተ ክርስቲያን፣ ባዶ ቤተ መንግስት  . . . ታሪክ ግን ብቻውን ቀረ፡፡ መልካም ስራቸውን እና ጉድለቶቻቸውን ገፅ በገፅ ይዞ ታሪክ በእያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ልብ ውስጥ ብቻውን ቀረ፡፡

2.     የስራ ባልደረባዬ ለዚች ሀገር (ዲ.ሪ. ኮንጎ) እንደእኔው እንግዳ ነው፡፡ ብዙ አፍሪካ ሀገሮች ላይ ንግድ ሰርቷል፡፡ እንደ ዲ.ሪ. ኮንጎ አይነት ለቢዝነስ ምቹ ሀገር የትም አይገኝም አለኝ፡፡ ምክንያቱን ስጠይቀው እንዲህ የሚል አስገራሚ መልስ ሰጠኝ "ህግ የሌለበት ሀገር ስለሆነ"፡፡

3.     ሮበን ቫን ፐርሲን የገዛው ትልቁ ማንቸስተር ዩናይትድ ተሸነፈ፡፡ ያስቃልም ያሳዝናልም፡፡

የግድ ነው፡፡ ሶስት ነገሮች ሳይከሰቱ ሶስት ቀኖች አያልፉም፡፡

No comments:

Post a Comment