Monday, September 16, 2013

አቦነሽ አድነው “አርቲስት” የሚለው መጠርያ ይገባታል?



ቀደም ሲል በተለየ ቅላፄዋና በባህል ሙዚቃዎቿ የምናውቃት አቦነሽ አድነው “ከዚህ በኋላ ዓለም ከአንደበቴ በሚወጣ ዘፈን አትደንስም ይልቁንስ ጩኸቴ፣ ቅኔ እና ዜማዬ የምስጋና ብቻ ነው” ብላ አዲስ የመዝሙር ስራዎቿን ይዛ ሰሞኑን ብቅ ማለቷ የሚመለከታቸውን ሰዎች ሁሉ ሲያነጋግር የሰነበተ ጉዳይ ነበር፡፡ መቼም ሰው ከአካባቢ ተፅንዖ፣ ከዓለም ዳንኪራ፣ ከከንቱ ውዳሴና ጭብጨባ አምልጦ  ሁለመናን ለፈጣሪ ሲሰጥ ማየት መንፈሳዊ ቅንዓት ከማሳደሩም በላይ ያበረታል፡፡ ይህን ስል ግን ዓላማዬ ያልተገባ የሰው ምስጋና ለአቦነሽ ለመስጠት ወይንም ብላቴናዋን ዘማሪት “ቅድስት” ብሎ ለመጥራት አይደለም፡፡