Saturday, April 27, 2013

አንዳንድ ብሽቅ ሰዎች




ቅዳሴ መሃል ነው፡፡ “በንሰሃ ውስጥ ያላችሁ ራሳችሁን ዝቅ ዝቅ አድርጉ” በሚለው የካህን ትዕዛዝ መሰረት በመቅደሱ ውስጽ ካሉት ጀምሮ ከደጀ ሰላሙ ቅጽር ውጪ እስካሉት ሰዎች ድረስ ግማሹ ከወገቡ ጎንበስ ከጉልበቱ ሸብረክ ብሎ የሁለት እጆቹን መዳፍ ለፈጣሪው እያሳየ ግማሹ ደግሞ በግንባሩ ተደፍቶ በፍፁም ፀጥታ ተውጠዋል፡፡ በድምፅ ማጉያው ከሚሰማው ከካህኑ የእግዚዮታ ድምፅ ውጭ ምንም ነገር አይሰማም አይንቀሳቀስም፡፡

Friday, April 26, 2013

ኢትዮጵያ ማለት እኔ ነኝ - ይድረስ ለኢትዮጵያ ፖለቲከኞች



ይድረስ በኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ ላልተደሰታችሁ እና ኢትዮጵያን እናንተ መልካም ነው ወዳላችሁት ጎዳና ለመውሰድ ለምትጥሩ የተቃዋሚም ሆነ የገዢው ፓርቲ ፖለቲከኞች፡፡

ይህ መልዕክት ያሰባችሁትን ሁሉ ለማሳካት ሊፈቅድላችሁም ሆነ ሊከለክላችሁ ከሚችለው ከመላ የኢትዮጵያ ህዝብ መሀል የአንዱ ድምፅ ነው፡፡