Friday, October 5, 2012

እኔ እግዚአብሔር እና ስሜ



በጭለማው መሃል ድንገት ተስፈንጥሮ ተነሳና ማብሪያ ማጥፊያውን ተጭኖ ጭለማውን ገሰሰው፡፡ አናቴ ደንግጣ እያማተበች በዚያ ለሊት የሚያፈጥባትን ሰውዬ መልሳ ትመለከተዋለች፡፡ “ምንድነው ይሔ?” አላት ሆዷን በሌባ ጣቱ እየጠነቆለ፡፡ እንደመተንፈስ አለችና “እኔንጃ” አለች ፊቱን ላለማየት አቀርቅራ፡፡ “እኔንጃ? ምንማለት ነው እኔንጃ? ኪኒን እንድትወስጂ ተስማምተን እየዋጥሽ አልነበር እንዴ?” በዚያ ፀጥ ባለ ሌሊት የእርሱ ድምፅ ብቻውን እንደመብረቅ ይጮሃል፡፡ “አዎ ኪኒኑንማ እየዋጥኩ ነው” አሁንም እንዳቀረቀረች ነው፡፡ “እና?!?!?” በይበልጥ አምባረቀ፡፡ ከዚህ በላይ መታገስ የምትችል አልመስል አላት ቢመታትም ጠንካራ ክንዱን ለመቻል ተዘጋጅታ “እንግዲህ ኪኒኑ አልሰራልኝም ማለት ነው ያለዚያማ እንዴት ልፀንስ እችላለሁ?” አለችው ተኮሳትራ፡፡ እንግዲህም ይህ ቅፅበት ነበር ለእኔ የህይወት መጀመርያ ለወላጆቼ ደግሞ የመጨረሻዋ ቀን የሆነችው፡፡ አቶ “አባት” እንደወጣ ሳይመለስ ቀረ የሰውና የጊዜ ክፉ የገጠማት እናቴም እኔን በሆዷ የሆነውን ሁሉ በልቧ ይዛ ብቸኛ ሆነች፡፡ አላማዬ የህይወት ታሪኬን ልነግራችሁ አይደለም የስሜን አመጣጥ ለማብራራት ይሔን ታሪክ መንገር ስላስፈለገኝ እንጂ፡፡

Thursday, October 4, 2012

የትኛው ድሮ



እድሜያቸው ዘጠና ዓመት የሞላቸውን አዛውንት ስለድሮ ብንጠይቃቸው ያለምንም ጥርጥር ከስልሳ አመት በፊት ስላለው ነገር ያጫውቱናል፡፡ የሀምሳ አመት ሽማግሌንም እንዲሁ ብንጠይቅ ከሀያ አምስት አመት በፊት ስላለው ጉዳይ ነው የሚነግሩን፡፡ ይህ ማለት እንግዲህ የድሮ ትርጉሙ እንደ አጫዋቹ ይለያያል ማለት ነው፡፡

Tuesday, October 2, 2012

በየቀኑ መታጠብ ዋና አያስችልም


ፈረስ መጋለብ የጀመርኩ ዕለት እንዴት ፈርቼ እንደነበር ልነግራችሁ አልችልም ግን ዕድሜ ለሃይሌ ሩት ጎትጉቶ ለወሰደኝ እና ላስተማረኝ ብዙም ሳልቆይ ነበር ያለፍርሃት በፍጥነት መጋለብ የጀመርኩት፡፡ ወዳጄ ፍቅሩ ታድያ አዲስ አበባ ውስጥ ፈረስ መጋለቢያ/መማርያ/ ቦታ እንዳለ ስነግረው በደስታ ነበር የፈነጠዘው፡፡ ችግሩ ግን ጊዜ አግኝቶ ይዠው ለመሔድ አለመቻሌ ነበር፡፡