Friday, September 28, 2012

ስደተኛ ቃላት



አንድ ቀን አዲስ አበባ ከጋናዊው ወዳጄ ጋር መረቅ የሆነ ጨዋታ እየተጫወትን በየአይነት እየበላን ነበር፡፡ ምሳችን ቢያልቅም ጫወታችንን ላለማቋረጥ አብረን ወደ እጅ መታጠቢያው እየተሳሳቅን አመራን፡፡ እጄን ወደ ውሃው ሰንዝሬ እየተለቃለቅኩ ቀድመውን ከሚታጠቡት ሰዎች መሀል አንደኛውን ሳሙናውን እንዲያቀብለን ጠየቅኩትና ወደጨዋታዬ ልመለስ ስል ይህ ጋናዊ ወዳጄ በመገረም አይነት ሰውየውን ምን እንዳልኩት በእንግሊዝኛ ጠየቀኝ እኔም ሳሙናውን አቀብለኝ እንዳልኩት በአማርኛ ስነግረው በጣም ተደንቆ ሳሙና የሚለውን ቃል እንደሚያውቀውና እሱ ከመጣበት ጋና ውስጥ ያለ አንድ ብሔርም በተመሳሳይ ይህንን መታጠቢያ ሳሙና ብለው እንደሚጠሩት ነገረኝ፡፡

የመጀመርያ


(በውሸት ታሪክ ላይ የተመሰረተ ዕውነተኛ ታሪክ)

ይህቺን ሚጢጢ ጥሁፍ እንድጥፋት የኮረኮረኝ ከባዱ ጦማሪ Naod ቤተሥላሴ በ “ናዖድ ኢትዮጵያዊ” ጦማሩ ላይ በአሜሪካ ሁሉ ነገር ‹‹የመጀመርያ› ባይሆንም በሚል ርዕስ አሜሪካኖች የመጀመሪያ ለመባል ትልልቅ ደንጊያዎችን እንዴት እንደሚያንከባልሉ ደስ በሚል ቋንቋ የገለፀውን ካነበብኩ በኋላ ነው፡፡ ናዖድ እንደገለፀው አሜሪካኖች ሩጫ ተወዳድሮ መጨረሻ ስለወጣ አሜሪካዊ ሯጭ ለመዘገብ መጀመርያአንደኛወይምየመጀመርያውየሚሆንበት መንገድ ይፈለግለታል፡፡ ከጥቂት ምርመራ በኋላ ወይ በዕድሜው፤ ወይ በጾታው፤ ወይ በትምህርት ደረጃው፤ ወይ በመጣበት ሀገር፤ ወይ መጨረሻ በወጣበት ሰዓት የመጀመሪያ ሰው እንደሆነ ሲረጋገጥ ‹‹በዚያ ሰዓት ለመግባት የመጀመርያው የሰባ ዓመት ዓዛውንት እንደሆነ ይዘገባል:: ታዲያ የናዖድን ፅሁፉን አንብቤ ስጨርስ ገጣሚ በዕውቀቱ ስዩም “በእኛ ቤት ታሪክ ውስጥ ሁለተኛ ልጅ በመሆን የመጀመሪያው ነኝ” ያለው ትዝ አለኝና ማሪኝ አሜሪካ አልኩ በልቤ::