Wednesday, August 15, 2012

ዜና ነገ ፩


የግብርና ሚኒስትሩ ስልጣናቸውን በፍቃዳቸው ለቀቁ፡፡

ሰኔ 29፣ 2015ዓ.ም (በኢትዮ. አቆጣጠር):- በትላንትናው ዕለት ለተወካዮች ም/ቤት የአመቱን የስራ አፈፃፀም ሪፖርት ያቀረቡት የግብርና ሚስትሩ የተከበሩ አቶ ብርሃን ባልቻ ሪፖርቱን ባቀረቡ ማግስት ስልጣናቸውን የመልቀቃቸውን ምክንያት ሲገልፁ "ሪፖርቱ ገበሬው በሚገባ ተጠቃሚ እንዳልነበር ያሳያል ስለዚህም የታቀደውን ያህል ልንፈፅም ስላልቻልን በፍቃዳችን ቦታውን ለሌሎች ማስረከብ ይኖርብናል" ሲሉ ለሪፖርተራችን ገልፀ  ል፡፡

የኢትዮጵያ አረጋውያን ከክፍያ ነፃ ሆኑ
ጥቅምት 21 ቀን 2009ዓ.ም (በኢትዮ. አቆጣጠር):- በጡረታ የተገለሉ እና በጦር ሜዳዎች ላይ የተካፈሉ አረጋውያን ከመብራት፣ ውሃ፣ ህክምና እና የትራንስፖርት አገልግሎት ክፍያ ነፃ መሆናቸውን የሚያበስረው አዋጅ ትላንት ጸደቀ፡፡ ለረዥም ጊዜ በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው ይህ አዋጅ ከሚቀጥለው ወር ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚሆን የሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዛሬ ባወጣው መግለጫ አመልክቷል፡፡

ዜና ነገ - እሺ! መፅሔትን እናዘጋጅ በነበረ ጊዜ በፍቅር እፅፋት የነበረች አነስተኛ አምድ ነች፡፡ በነገይቱ ብሩህ ኢትዮጵያ ውስጥ ማየት የምመኘውን የምፅፍበት ነፃ ግዛቴ ነው::

No comments:

Post a Comment