ደህና ሁኚ Get link Facebook X Pinterest Email Other Apps - August 07, 2019 የተሳሰርንበትን ገመድ ከበጠስሽው ዘንዳ፣ ሂጂ ብረሪ ክንፎችሽን ዘረጋግተሽ ተንጠራሪ፣ ነፃ ነሽና ፈንጥዢ። ገመድ የለም ከደረቴ፣ ያሰርኩበት ሲባጎም የለምና ከእጄ ሂጂ ብረሪ ክንፎችሽን ዘረጋግተሽ ተንጠራሪ፣ ነፃ ነሽና ፈንጥዢ። የት ሄደች ካሉኝ ፈታኋት እላቸዋለሁ። Get link Facebook X Pinterest Email Other Apps Comments
አከራዮቼ 1 - November 01, 2012 እንደው መታደል ሆኖ ከኢትዮጵያዊ እናት ተፈጠርኩኝ እንጂ ወላጆቼ ፈርዶባቸው ፈረንጅ ቢሆኑ ኖሮ እድሜዬ ለአቅመ ሸክም በደረሰ በዚያ ወቅት (በ19 ዓመቴ ማለት ነው) “ሌላ ቤት ተከራይ አሊያም ኪራይ ክፈል” ይሉኝ ነበር፡፡ ያን ጊዜ ግን እኔ ራሴን መቻል ያሰኘኝ ወቅት ስለነበር እናቴን ሔጄ " ራሴን አሸክሚኝ" ስላት አንድ ቃል ነበር ከአፏ የወጣው “አትቅበጥ” የሚል፡፡ አዲስ ቦታ፣ አዲስ ሰው፣ አዲስ ነገር ሁሉ ደስ ይለኛል፡፡ አንድ ነገር ወይንም አንድ ቦታ ላይ ችክ ማለት አልችልበትም፡፡ ስልቹ ነገር ነኝ፡፡ የምሰራበት ቦታ ላይ ሁልጊዜ አዳዲስ ነገሮችን መፍጠር ካልቻልኩ ቀኑን መግፋት ያቅተኛል፡፡ ተደጋጋሚ(Routine) ነገሮችን እንደመፈፀም የሚያሳምመኝ ነገር እስካሁን የለም፡፡ ለነገሩ ስራ ላይ ብቻ ሳይሆን ቤት ኪራይ ላይም እንዲሁ ነኝ፡፡ ባለፉት በአስር አመታት ውስጥ እንኳን ስምንት ቤቶችን ለዋውጫለሁ፡፡ ኪራይ እስከሆነ ድረስ ምን አንድ ቦታ ላይ አስቸከለኝ? ሙሉውን አስነብበኝ »
አንዳንድ ብሽቅ ሰዎች - April 27, 2013 ቅዳሴ መሃል ነው፡፡ “በንሰሃ ውስጥ ያላችሁ ራሳችሁን ዝቅ ዝቅ አድርጉ” በሚለው የካህን ትዕዛዝ መሰረት በመቅደሱ ውስጽ ካሉት ጀምሮ ከደጀ ሰላሙ ቅጽር ውጪ እስካሉት ሰዎች ድረስ ግማሹ ከወገቡ ጎንበስ ከጉልበቱ ሸብረክ ብሎ የሁለት እጆቹን መዳፍ ለፈጣሪው እያሳየ ግማሹ ደግሞ በግንባሩ ተደፍቶ በፍፁም ፀጥታ ተውጠዋል፡፡ በድምፅ ማጉያው ከሚሰማው ከካህኑ የእግዚዮታ ድምፅ ውጭ ምንም ነገር አይሰማም አይንቀሳቀስም፡፡ ሙሉውን አስነብበኝ »
Comments
Post a Comment