Monday, July 30, 2012

አጫጭር ትንፋሾች ፪



ድንገት ነቃ፡፡ የተጀቦነበትንም የፍልስፍና ድሪቶ ከላዩ ገፈፍ አድርጎ አይኑን የሚወጋውን ብርሀን ሊቋቋም እየሞከረ አለምን በግርማሞት መንፈስ አያት፡፡ ዙርያ ጥጉንም ሲገረምም አንዳችም ነፍስ ጎኑ የለም ቢሆንም ብዙም አልተደነቀም፡፡ ምክንያቱም የኔ የሚላቸው ነፍሶች ዞረው ለአለም አግዘው ሲያቆስሉት በተደጋጋሚ ታዝቧልና፡፡ እንግዲህ ከዚህ በኋላ ነው ወፋፍራም ግን አጫጭር ትንፋሾች ጉሮሮውን እየቧጠጡት ሳያውቀው እንዲህ የሚል ድምፅ ያወጣው " . . . ይሻለኛል ችጋር፡፡ ከመቶ እጥፍ በላይ ርሃብ ይሻኛል፡፡ ቁርበቴ ገርጥቶ አጥንቶቼ ገጠው ብውል፣ ባድር፣ ብኖር ይሻለኛል፡፡ በቁራሽ እንጀራ እጦት አንጀቴ ተላውሶ በችንጋር አለንጋ ብጠበስ ብቆላ ለእኔ ይሻለኛል፡፡ ጉንጭ ውሃ አጥቼ ምላስ ከትናጋዬ ቢጣበቅ ከንፈሮቼም ደርቀው ኩበትን ቢያስንቁ እመርጣለሁ፡፡ ይህ ሁሉ ስለ ተስፋ ይሆናል፡፡ ተስፋ አጥቼ ከምኖር አለም ሁሉ ብትቀርብኝ አይጎዳኝም፡፡ ያለ ተስፋ ከመባዘን፣ ሞት የጀግና ዕረፍት ነው ለእኔ፡፡ ተስፋን ከማጣ የምበላው እህል ባጣ እንኳ ግድ አይለኝም እኔ፡፡ ያለ ገንዘብ መኖር እችላለሁ፣ ያለ ተስፋ ግን እስትንፋስ የሌለኝ ደረቅ እንጨት ነኝ፡፡ " ተመልሶ ተጠቅልሎ ተጋደመ እኔም አልቀሰቀስኩትም::


(ኪንሻሳ - ዲ.ሪ ኮንጐ )

No comments:

Post a Comment