Posts

Showing posts with the label Ethiopia

አቦነሽ አድነው “አርቲስት” የሚለው መጠርያ ይገባታል?

Image
ቀደም ሲል በተለየ ቅላፄዋና በባህል ሙዚቃዎቿ የምናውቃት አቦነሽ አድነው “ከዚህ በኋላ ዓለም ከአንደበቴ በሚወጣ ዘፈን አትደንስም ይልቁንስ ጩኸቴ፣ ቅኔ እና ዜማዬ የምስጋና ብቻ ነው” ብላ አዲስ የመዝሙር ስራዎቿን ይዛ ሰሞኑን ብቅ ማለቷ የሚመለከታቸውን ሰዎች ሁሉ ሲያነጋግር የሰነበተ ጉዳይ ነበር፡፡ መቼም ሰው ከአካባቢ ተፅንዖ፣ ከዓለም ዳንኪራ፣ ከከንቱ ውዳሴና ጭብጨባ አምልጦ  ሁለመናን ለፈጣሪ ሲሰጥ ማየት መንፈሳዊ ቅንዓት ከማሳደሩም በላይ ያበረታል፡፡ ይህን ስል ግን ዓላማዬ ያልተገባ የሰው ምስጋና ለአቦነሽ ለመስጠት ወይንም ብላቴናዋን ዘማሪት “ቅድስት” ብሎ ለመጥራት አይደለም፡፡

ዳግም ትንሳዔ???

Image
የጠቅላይ ሚኒስትራችንን ጤንነት በተመለከተ ባለፉትን አርባ አምስት ቀናት ይዘገቡ የነበሩ ዜናዎች እና ከወዲህ ወዲያ የተሰነዘሩት አስተያየቶች እርስበርሳቸው የተጣረሱ ከመሆናቸው ባሻገር የብዙ ለውጥ ፈላጊዎችን ደም ሞቅ ያደረገ ሁኔታ ሆኖ ተስተውሏል፡፡ ነፃ የመተንፈሻ ሚዲያ ያጣው የኢትዮጵያ ህዝብም በየፊናው ሆኖ የየራሱን ስሜትና ምኞት ባገኘው የማህበራዊ ድረ ገፅ ላይ መለጠፉን ተያይዞታል፡፡ አንዱ አዋቂ "ጠ/ሚሩ ከሞቱ 2 ሳምንት አለፋቸው" ሲል ሌላኛው አዋቂ ደግሞ "ንጉሳችን በድል አ/አ ገቡ" ይላል፡፡ አንደኛው የዜና አውታር "ጠ/ሚሩ ከጭንቅላት ጋር የተገናኘ ህመም ይዟቸዋል" ሲለን ሌላኛው ከመቅፅበት "የለም እሳቸውን ካልጋ ያስተዋወቀው የቆየ የሆድ ህመማቸው ነው" ይለናል፡፡ በተለይ ፌስቡክ እና ትዊተር ድረ ገፆች የተቻላቸውን ያህል የየሰውን ስሜት ሲያስተጋቡ ከረመዋል፡፡ ከአንዴም ሶስት ጊዜ ህልፈታቸው በደማቅ አራት ነጥቦች ታጅቦ ታውጇል፡፡ ያንኑ ያህል ግዜም ባይኔ በብረቱ አይቻቸዋለሁ በሚመስል ድፍረት "ሰውየው አዲስ አበባ ምኒልክ ቤ/መ ውስጥ ጋቢ ደረብ አድርገው ሶፋቸው ላይ ጋደም ብለው ሲ ኤን ኤን ከፍተው ዘ ኢኮኖሚስትን እያነበቡ አጃ ነገር እየጠጡ ነው" ያለም አልጠፋም፡፡ ይህ ሁሉ ሲሆን ግን እንደሰከረ ሰው ከመዘላበድ ውጪ አንድም የመንግስት አካል በግልፅ ስለጠቅላይ ሚኒስትሩ ጤንነት ማብራርያ መስጠት አልደፈሩም፡፡